ቀሪ (አንባቢ)
የንባብ ዘዴ
1
ዝርዝር መረጃ
وَالسَّمَاءِ ذَاتِ الْبُرُوجِ
የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَـٰنِ الرَّحِيمِ
وَالسَّمَاءِ ذَاتِ الْبُرُوجِ
የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
2
ዝርዝር መረጃ
وَالْيَوْمِ الْمَوْعُودِ
በተቀጠረው ቀንም፤
وَالْيَوْمِ الْمَوْعُودِ
በተቀጠረው ቀንም፤
3
ዝርዝር መረጃ
وَشَاهِدٍ وَمَشْهُودٍ
በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡
وَشَاهِدٍ وَمَشْهُودٍ
በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡
4
ዝርዝር መረጃ
قُتِلَ أَصْحَابُ الْأُخْدُودِ
የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡
قُتِلَ أَصْحَابُ الْأُخْدُودِ
የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡
5
ዝርዝር መረጃ
النَّارِ ذَاتِ الْوَقُودِ
የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡
النَّارِ ذَاتِ الْوَقُودِ
የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡
6
ዝርዝር መረጃ
إِذْ هُمْ عَلَيْهَا قُعُودٌ
እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡
إِذْ هُمْ عَلَيْهَا قُعُودٌ
እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡
7
ዝርዝር መረጃ
وَهُمْ عَلَىٰ مَا يَفْعَلُونَ بِالْمُؤْمِنِينَ شُهُودٌ
እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡
وَهُمْ عَلَىٰ مَا يَفْعَلُونَ بِالْمُؤْمِنِينَ شُهُودٌ
እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡
8
ዝርዝር መረጃ
وَمَا نَقَمُوا مِنْهُمْ إِلَّا أَن يُؤْمِنُوا بِاللَّهِ الْعَزِيزِ الْحَمِيدِ
ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡
وَمَا نَقَمُوا مِنْهُمْ إِلَّا أَن يُؤْمِنُوا بِاللَّهِ الْعَزِيزِ الْحَمِيدِ
ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡
9
ዝርዝር መረጃ
الَّذِي لَهُ مُلْكُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ وَاللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ شَهِيدٌ
በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡
الَّذِي لَهُ مُلْكُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ وَاللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ شَهِيدٌ
በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡
10
ዝርዝር መረጃ
إِنَّ الَّذِينَ فَتَنُوا الْمُؤْمِنِينَ وَالْمُؤْمِنَاتِ ثُمَّ لَمْ يَتُوبُوا فَلَهُمْ عَذَابُ جَهَنَّمَ وَلَهُمْ عَذَابُ الْحَرِيقِ
እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡
إِنَّ الَّذِينَ فَتَنُوا الْمُؤْمِنِينَ وَالْمُؤْمِنَاتِ ثُمَّ لَمْ يَتُوبُوا فَلَهُمْ عَذَابُ جَهَنَّمَ وَلَهُمْ عَذَابُ الْحَرِيقِ
እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡
11
ዝርዝር መረጃ
إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ لَهُمْ جَنَّاتٌ تَجْرِي مِن تَحْتِهَا الْأَنْهَارُ ۚ ذَٰلِكَ الْفَوْزُ الْكَبِيرُ
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡
إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ لَهُمْ جَنَّاتٌ تَجْرِي مِن تَحْتِهَا الْأَنْهَارُ ۚ ذَٰلِكَ الْفَوْزُ الْكَبِيرُ
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡
12
ዝርዝር መረጃ
إِنَّ بَطْشَ رَبِّكَ لَشَدِيدٌ
የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡
إِنَّ بَطْشَ رَبِّكَ لَشَدِيدٌ
የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡
13
ዝርዝር መረጃ
إِنَّهُ هُوَ يُبْدِئُ وَيُعِيدُ
እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡
إِنَّهُ هُوَ يُبْدِئُ وَيُعِيدُ
እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡
14
ዝርዝር መረጃ
وَهُوَ الْغَفُورُ الْوَدُودُ
እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡
وَهُوَ الْغَفُورُ الْوَدُودُ
እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡
15
ዝርዝር መረጃ
ذُو الْعَرْشِ الْمَجِيدُ
የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡
ذُو الْعَرْشِ الْمَجِيدُ
የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡
16
ዝርዝር መረጃ
فَعَّالٌ لِّمَا يُرِيدُ
የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡
فَعَّالٌ لِّمَا يُرِيدُ
የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡
17
ዝርዝር መረጃ
هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ الْجُنُودِ
የሰራዊቶቹ ወሬ መጣልህን?
هَلْ أَتَاكَ حَدِيثُ الْجُنُودِ
የሰራዊቶቹ ወሬ መጣልህን?
18
ዝርዝር መረጃ
فِرْعَوْنَ وَثَمُودَ
የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡
فِرْعَوْنَ وَثَمُودَ
የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡
19
ዝርዝር መረጃ
بَلِ الَّذِينَ كَفَرُوا فِي تَكْذِيبٍ
በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡
بَلِ الَّذِينَ كَفَرُوا فِي تَكْذِيبٍ
በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡
20
ዝርዝር መረጃ
وَاللَّهُ مِن وَرَائِهِم مُّحِيطٌ
አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡
وَاللَّهُ مِن وَرَائِهِم مُّحِيطٌ
አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡
21
ዝርዝር መረጃ
بَلْ هُوَ قُرْآنٌ مَّجِيدٌ
ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
بَلْ هُوَ قُرْآنٌ مَّجِيدٌ
ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
22
ዝርዝር መረጃ
فِي لَوْحٍ مَّحْفُوظٍ
የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡
فِي لَوْحٍ مَّحْفُوظٍ
የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡